Fana: At a Speed of Life!

ጥቅምት 24 ሲታወስ ሀገራዊ ህልውናን በማረጋገጥ ታሪክ የሰሩ ጀግኖችን በማሰብ መሆን አለበት – ሌ/ጄ ዘውዱ በላይ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጥቅምት 24 ሲታወስ ህግ በማስከበርና ሀገራዊ ህልውናን በማረጋገጥ ታሪክ የሰሩ ጀግኖችን በማሰብ መሆን አለበት አሉ የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ዘውዱ በላይ።

በሀገር መከላከያ ሠራዊት ሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት የተፈፀመበት 5ኛ ዓመት “እንዳይደገም ፤ መቼም አንረሳውም” በሚል መሪ ሃሳብ የማዕከላዊ ዕዝ አመራሮች፣ አባላት እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት በፓናል ውይይት በጅማ ከተማ ታስቧል።

በመድረኩ ላይ የሠራዊቱ አባላት፤ ሠራዊቱ ላይ የተፈጸመው ጥቃት ብዙ ምስቅልቅል ማስከተሉን አስታውሰው፤ የሰላምን ዋጋ መገንዘብ ይገባል ብለዋል።

ሠራዊቱ ላይ የደረሰው በደል እንዳይደገም በትጋት መስራት እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል።

የዕዙ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ዘውዱ በላይ በበኩላቸው፤ ቀኑ ሲታሰብ በወቅቱ የተፈጠረውን ሁኔታ በመኮነን፣ በክህደት ከጀርባቸው ተወግተው መስዋዕት የሆኑ የሠራዊት አባላትን በማስታወስ መሆን አለበት ብለዋል።

ህግ በማስከበርና የሀገር ህልውናን በማረጋገጥ ታሪክ የሰሩ የሰራዊት አባላትን ጀግንነት በማውሳት መሆን እንዳለበትም አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ህዝብ ጥቃቱን ለመቀልበስ ያሣየው አለኝታነት የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰው፤ ምስጋና አቅርበዋል።

በአቤንኤዘር ታየ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.