Fana: At a Speed of Life!

የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በመዲናዋ የልማት ሥራዎችን እየጎበኙ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በአዲስ አበባ ከተማ የተሰሩ የልማት ሥራዎችን እየጎበኙ ነው።

የአመራሮቹ ጉብኝት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሙዚየም፣ የኢሬቻ ፓርክ፣ የአራዳ ፓርክ እና የላፍቶ የገበያ ማዕከልን ጨምሮ ሌሎች በከተማዋ የተሰሩ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶችን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።

ፕሮጀክቶቹ መንግሥት የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፍላጎቶችን በተገቢው መንገድ ለመመለስ የሚያደርገውን ጥረት የሚያሳዩ መሆናቸውም ተመላክቷል።

የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች በጉብኝቱ ወቅት መሬት ላይ በተተገበሩ ፕሮጀክቶች ፀጋን ለይቶ በማልማት ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ እንዴት እንደሚቻል በተግባር እንዲመለከቱ ለማድረግ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።

የብልጽግና ፓርቲ የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የከፍተኛ አመራር ስልጠና በአዳማ ከተማ እየተሰጠ መቆየቱ ይታወቃል።

በአንዷለም ተስፋዬ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.