ፕሬዚዳንት ታዬ በላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ሕልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በታሪክ ተመራማሪው ላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ሕልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገልጸዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት የሐዘን መግለጫ መልዕክት ÷ ላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው ጥልቅ ሐዘኔን እገልጻለሁ ብለዋል፡፡
ላጲሶ (ፕ/ር) በኢትዮጵያ የሥነ መንግሥት ታሪክ ምርምርና የላቀ የዕውቀት ሥርፀት ላደረጉት አስተዋፅኦ ሲታወሱ ይኖራሉ ነው ያሉት፡፡
ለቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸውም መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!