ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት ቱሪዝም ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ እየተሳተፈች ነው
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የቱሪዝም ድርጅት 26ኛ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ እየተሳተፈች ነው፡፡
በጉባዔው በቱሪዝም ሚኒስትር ዴዔታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) የተመራ ልዑክና በሳዑዲ ዓረቢያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር ከድር (ዶ/ር) ተሳትፈዋል፡፡
ከጥቅምት 28 እስከ ሕዳር 2 ቀን 2018 ዓ.ም በሪያድ እየተካሄደ በሚገኘው ጉባዔ ከ160 አባል ሀገራት የተወጣጡ ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለስልጣናትና ሌሎች እንግዶች ታድመዋል።
መድረኩ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘላቂና ሁሉን አቀፍ እድገትን ማፋጠን በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ለመምከር ያለመ ነው፡፡
በተጨማሪም በቱሪዝም ዘርፍ ዓለም አቀፍ ትብብርን ማጠናከር እንደሚያስችል ነው የተገለጸው፡፡
ጉባዔው በኢትዮጵያ በከፍተኛ ትኩረት እየተሰራበት የሚገኘውን የቱሪዝም ዘርፍ ይበልጥ ለማሳደግ ልምድ የሚቀሰምበት እንደሚሆን ተመላክቷል፡፡
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!