Fana: At a Speed of Life!

የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን አጠናቅቀው ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ኢብራሂም በኢትዮጵያ ያደረጉትን የሦስት ቀናት የስራ ጉብኝት አጠናቅቀው ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አሸናኘት አድርገውላቸዋል።

በኢትዮጵያ ቆይታቸው በብሔራዊ ቤተመንግሥት ይፋዊ የአቀባበል ሥነ ሥርዓት የተደረገላቸው የማሌዢያው ጠቅላይ ሚኒስትር÷ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር ውይይት አድርገዋል።

መርሐ ግብሩ የወዳጅነት ዛፍ የመትከል ሥነ ሥርዓት፣ የብሔራዊ ቤተመንግሥት ጉብኝት፣ የሁለትዮሽ ውይይት፣ የሰነዶች ልውውጥ ብሎም በቱሪዝም፣ ጤና፣ አየር ትራንስፖርት አገልግሎት፣ በኳላ ላምፑር ከተማ ምክር ቤት እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትብብር ስምምነቶችን ያካተተ ነበር።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባለፈው ዓመት በማሌዥያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡

በለይኩን ዓለም

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Facebook https://web.facebook.com/fanasport
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.