Fana: At a Speed of Life!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ለሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር በብሔራዊ ቤተ መንግሥት አቀባበል አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ በብሔራዊ ቤተመንግሥት ይፋዊ የአቀባበል ሥነ ሥርዓት አካሂደዋል።

የአቀባበል ሥነ ሥርዓቱ ወዳጅነትን የሚያመላክት የዛፍ መትከል መርሐ ግብር፣ የብሔራዊ ሙዚዬም ታሪካዊ ቁሶች እና ምድረግቢ ጉብኝትን ያካተተ ነው፡፡

በተጨማሪም የሁለትዮሽ ውይይቶችና በክሕሎት ልማት እና የካርበን ብድር የመግባቢያ ስምምነቶች ፊርማን አስቀድሞ የጋራ ጋዜጣዊ መግለጫን ያካተተ እንደነበር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትር ዋንግ ጉብኝት በሰኔ 2017 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በሲንጋፖር ያደረጉትን ጉብኝት ተከትሎ የተካሄደ ሲሆን÷ ይህም በሁለቱ ሀገራት መካከል እያደገ የመጣውን ግንኙነት ያሳያል፡፡

ሁለቱ መሪዎች በጉብኝቱ የኢኮኖሚ ትብብርን ለማላቅ፣ ተቋማዊ መስተጋብርን ለማጠናከርና የወል ቅድሚያዎቻቸውን ከፍ አድርጎ ለመከወን መንገዶችን እንደተመለከቱ ተጠቅሷል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.