Fana: At a Speed of Life!

ታማኝ ግብር ከፋዮች ገበያን በማረጋጋት ረገድ የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል – ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ታማኝ ግብር ከፋዮች ገበያን በማረጋጋት ረገድ የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል አሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት 3ኛ ዙር የግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች የእውቅና እና ሽልማት መርሐ ግብር ተካሂዷል።

ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት ÷ ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ ካደጉ ሀገራት ተርታ እንድትሰለፍ ለማድረግ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡

በክልሉ በግብርና፣ ኢንዱስትሪና በሌሎች ዘርፎች የሚሳተፉ አልሚዎችን የማበረታታቱና የመደገፉ ሥራ ተጠናከሮ ይቀጥላል ነው ያሉት፡፡

ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች በመሆን እውቅናና ሽልማት የተበረከተላቸው ታማኝ ግብር ከፋዮች ብቻ ሳይሆኑ አምራች፣ አቅራቢና ገበያ የሚያረጋጉ ናቸው ሲሉ አውስተዋል፡፡

በክልሉ በተለያዩ ዘርፎች መሰማራት ለሚፈልጉ ባለሃብቶች ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ጠቁመው÷ አልሚዎች ዕድሉን በመጠቀም በልማት ሥራዎች ላይ እንዲሳተፉ ጠይቀዋል፡፡

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ሕይወት አሰግድ በበኩላቸው÷ በክልሉ የሚሰበሰበው ገቢ በቴክኖሎጂ የታገዘ እንዲሆን የተለያዩ የአሰራር ሥርዓቶች እየተዘረጉ ነው ብለዋል፡፡

ክልላዊ የገቢ አቅሞችን በጥናት በመለየት የገቢ አፈጻጸምን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ማለታቸውንም የክልሉ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሃላፊ የሽዋስ አለሙ ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል።

በዮናስ ጌትነት

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.