Fana: At a Speed of Life!

በደሴ ከተማ በደረሰ የመኪና አደጋ የ3 ሰዎች ህይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአማራ ክልል ደሴ ከተማ በደረሰ የመኪና አደጋ የ3 ሰዎች ህይወት አልፏል።

በከተማዋ ሰኞ ገበያ ክፍለ ከተማ ቢለን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በደረሰ የመኪና አደጋ የ3 ሰዎች ህይወት ማለፉን በደሴ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የ3ኛ ፖሊስ ጣቢያ ኃላፊ ኢንስፔክተር ፈቲያ ሀሰን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል።

አደጋው በዛሬው ዕለት ከቀኑ 10 ሰዓት አካባቢ የደረሰ መሆኑን ነው የገለጹት።

አደጋው የጭነት ተሽከርካሪ መኪና በመገልበጡ ምክንያት መከሰቱን አንስተው÷ የ3 ሰዎች ህይወታቸው ሲያልፍ 2 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት እንደደረሰ አስረድተዋል።

በአደጋው በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን የገለጹት ኃላፊዋ÷ የተሽከርካሪው ሹፌር በህግ ስር ሆኖ ህክምና እየተከታተለ መሆኑን አውስተው÷ የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑን አመላክተዋል።

በከድር መሀመድ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Facebook https://web.facebook.com/fanasport
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.