Fana: At a Speed of Life!

ኮሚሽኑ በኢትዮጵያ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ይበጃሉ ያላቸውን አጀንዳዎች የልየታ ስራ እያጠናቀቀ ነው – መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በኢትዮጵያ የቆዩ ችግሮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ይበጃሉ ያላቸው አጀንዳዎች የልየታ ስራ እየተጠናቀቀ ነው አሉ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)።

ኮሚሽኑ በእስካሁን ሂደት የተከናወኑ ተግባራትንና የተገኙ ውጤቶችን ለዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ገለጻ እያደረገ ይገኛል።

በመርሐ ግብሩ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነሮች፣ አምባሳደሮች፣ ተቀማጭነታቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።

ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) በዚሁ ወቅት÷ ሀገራዊ ዘላቂ ሰላም፣ መረጋጋትና ዴሞክራሲን ለማስፈን በምክክር ላይ የተመሰረተ መፍትሔ ለማምጣት እየተሰራ ነው ብለዋል።

ለዚህም ኮሚሽኑ የሁሉም ድምጽ የሚሰማበት አካታችና አሳታፊ ሂደትን እየተከተለ እንደሚገኝ ገልጸው÷ ነጻ፣ ገለልተኛና ተዓማኒነት ያላቸው አሰራሮችን በመከተል ሥራውን እያከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በሂደቱም አሳታፊ በሆነ መንገድ በኢትዮጵያ በቆዩ ችግሮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ይበጃሉ የተባሉ አጀንዳዎች ልየታ ስራን እያጠናቀቀ መሆኑን አስረድተዋል።

የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ስራው ውጤታማ እንዲሆን መስራት ሌላው የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን መግለፃቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Facebook https://web.facebook.com/fanasport
Facebook WMCC
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.