Fana: At a Speed of Life!

የፊፋ ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ክስ ቀረበባቸው

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማሕበር (ፊፋ) ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡

የፊፋው ፕሬዚዳንት ክስ የቀረባበቸው የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባሸነፉት የፊፋ የሰላም ሽልማት ስለመሆኑ ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡

ፕሬዚዳንቱ የሰላም ሽልማቱን ሲያዘጋጁ የተቋሙን ኮሚቴ እንዲሁም ምክትል ፕሬዚዳንቱን አለማማከራቸው የተገለጸ ሲሆን÷ የፊፋን የፖለቲካ ገለልተኝነት በተደጋጋሚ መጣሳቸው ተመላክቷል፡፡

የሥነ ምግባር ኮሚቴው የፊፋ የሰላም ሽልማትን ለማስተዋወቅና ለመሸለም በተደረገው ውሳኔ ዙሪያ ከፊፋ የሥርዓት ህጎች ጋር የተጣጣሙ መሆናቸውን እንዲመረምር ጠይቋል።

ትራምፕ የሰላም ሽልማትን የተቀበሉት ባሳለፍነው አርብ በዋሽንግተን ዲሲ በተካሄደው የፊፋ 2026 የዓለም ዋንጫ የዕጣ ድልድል ማውጣት ሥነ ሥርዓት ላይ እንደነበር አይዘነጋም፡፡

በወቅቱም ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ለአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋንጫ፣ ሜዳሊያ እና የምስክር ወረቀት ማበርከታቸው ይታወሳል፡፡

ፊፋ የሰላም ሽልማቱን ያዘጋጀው ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑ ይታወቃል፡፡

በወንድማገኝ ፀጋዬ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Facebook https://web.facebook.com/fanasport
Facebook WMCC
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.