ኢትዮጵያ 5ኛውን የአፍሪካ ወጣቶች ኦሊምፒክ ጨዋታ እንድታዘጋጅ ተመረጠች
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ 5ኛውን የአፍሪካ ወጣቶች ኦሊምፒክ ጨዋታ እንድታዘጋጅ ተመርጣለች፡፡
4ኛው የአፍሪካ ወጣቶች ኦሊምፒክ ጨዋታ እየተደረገ በሚገኝባት አንጎላ ሉዋንዳ ከተማ በተደረገ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የኢትዮጵያ ውድድሩን የማዘጋጀት ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡
የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ኢትዮጵያ 5ኛውን የወጣቶች ኦሊምፒክ ጨዋታ በማዘጋጀት ዙሪያ ለጠቅላላ ጉባኤው ንግግር አድርገዋል።
ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸውም የኢትዮጵያ መንግሥት እና ሕዝብ ይህንን ትልቅ አሕጉራዊ ውድድር ለማዘጋጀት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለው አብራርተዋል፡፡
በጥያቄው መሠረትም ጠቅላላ ጉባኤው የኢትዮጵያን የማዘጋጀት ጥያቄ በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል።
በሙባረክ ፋንታው
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Facebook https://web.facebook.com/fanasport
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!