በአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በዛሬው ዕለት አራት የምድብ ማጣሪያ ሁለተኛ ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡
ምሽት 5 ሰዓት ላይ በምድብ ሶስት የተደለደሉት ናይጄሪያና ቱኒዚያ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
ቡድኖቹ የምድብ ማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታቸውን በድል መወጣታቸው ይታወሳል።
ከዚህ ጨዋታ አስቀድሞ ምሽት 2:30 ላይ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታቸው ሽንፈት ያስተናገዱት ኡጋንዳ እና ታንዛኒያ ይገናኛሉ።
በምድብ አራት የተደለደሉት ቤኒን እና ቦትስዋና ቀን 9:30 ሲገናኙ፤ ሴኔጋል እና ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አመሻሽ 12:00 ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ትናንት በተካሄደ ጨዋታ ግብጽ ደቡብ አፍሪካን 1 ለ 0 ስታሸንፍ፤ አንጎላ እና ዚምባቡዌ 1 ለ 1፣ ዛምቢያ እና ኮሞሮስ 0 ለ 0 እንዲሁም አዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ እና ማሊ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት መለያየታቸው ይታወቃል።