Fana: At a Speed of Life!

የዲሜ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ ”ቤትኽ” በዓል እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዲሜ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ ”ቤትኽ” በዓል በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ነው፡፡

የሳላማጎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ህጉ ቅጣቱ ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት÷ ኢትዮጵያ በበርካታ ልዩነት ውስጥ አንድነቷን አስጠብቃ የቆየች ሀገር መሆኗን አውስተዋል፡፡

የዲሜ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ ”ቤትኽ” የመቻቻልና የአብሮነት በዓል መሆኑን ጠቅሰው ÷ በዓሉ ከሌሎች ወንድም የኢትዮጵያ ሕዝቦች ጋር በጋራ እየተከበረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በወረዳው ያልተዳሰሱ በርካታ ቱባ ባህሎች መኖራቸውን የገለጹት ዋና አስተዳዳሪው ÷ እሴቶቹ ለጥናትና ምርምር እንዲሁም ለቱሪስት መዳረሻነት ክፍት መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ በበኩላቸው ÷ በዓሉ የተጣላ የሚታረቅበትና አብሮነት የሚጠናከርበት እንዲሁም አባቶች ትውልዱን የሚመርቁበት ነው ብለዋል፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል አጉ ደባን ÷ የማሕበረሰቡን መልካም እሴቶች በጥናት በማስደገፍ ለዓለም ማሕበረሰብ ለማስተዋወቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

”ቤትኽ” የዲሜ ብሔረሰብ ካለፈው ስህተታቸው ተምረው ለተሻለ እድገት የሚሰናዱበት፣ ቂምና ጥላቻን የሚሽሩበትና ፈጣሪያቸውን የሚያመሰግኑበት በዓል መሆኑን የደቡብ ኦሞ ዞን ኮሙኒኬሽን ቢሮ ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.