ሴኔጋል ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሴኔጋል ሱዳንን 3 ለ 1 በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች።
ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተካሄደው የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ሴኔጋል ፓፔ ጉዬ (ሁለት) እና ምባዬ ባስቆጠሯቸው ሶስት ግቦች ሱዳንን አሸንፋለች።
ሱዳን ከሽንፈት ያልታደጋትን ብቸኛ ግብ አሚር አብደላህ ከመረብ አሳርፏል።
ጨዋታው ምሽት 4 ሰዓት ላይ ቀጥሎ ሲካሄድ ማሊ እና ቱኒዚያ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል።