Fana: At a Speed of Life!

ግብፅ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ግብፅ ቤኒንን 3 ለ 1 በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች፡፡

የግብፅን የማሸነፊያ ግቦች ሳላህ፣አቴያ እና ኢብራሂም ሲያስቆጥሩ ቤኒንን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ደግሞ ዶሱ ከመረብ አሳርፏል፡፡

ጨዋታው ቀጥሎ ሲካሄድ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ናይጄሪያ ከሞዛምቢክ ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

ግብፅ አዘጋጇ ሀገር ሞሮኮን ፣ካሜሩን ፣ሴኔጋል እና ማሊን በመከተል ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀለች አምስተኛዋ ሀገር ሆናለች፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.