Fana: At a Speed of Life!

የአእላፋት ዝማሬ መንፈሳዊ ትዕይንት አስደናቂ ነበረ – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በገና ዋዜማ በመስቀል ዐደባባይ የቀረበው የአእላፋት ዝማሬ መንፈሳዊ ትዕይንት አስደናቂ ነበረ አሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማሕበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷ ወጣቶች ጨዋነት እና ሥነ ሥርዓት በሞላበት መንገድ ሃይማኖታቸውን መግለጣቸው ስለ መጪው ትውልድ ያለንን አመለካከት የሚቀይር ነው ብለዋል።

ትውልዱ ዕድሉ ከተሰጠው ከአስፈሪና አስጊ ነገሮች ርቆ መልካም የሆነውን መንገድ እንደሚከተል አሳይተዋልም ነው ያሉት።

የሃይማኖት እንቅስቃሴዎች የራስን በመግለጥ፣ ሌላውን በማክበርና የጋራ ዕሴት በመፍጠር ላይ ከተመሠረቱ ለሀገር የሚያስገኙት ዋጋ ከፍ ያለ እንደሆነም አመላክተዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Facebook https://web.facebook.com/fanasport
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.