በጤና ቁጥጥር ሥርዓት ላይ ያተኮረ ሀገር አቀፍ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው
የጤና ሚኒስትር ዴዔታ ፍሬሕይወት አበበ በዚህ ወቅት እንዳሉት ፥ በመከላከልና አክሞ ማዳን ላይ ትኩረት ያደረገው የጤና ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆን ጠንካራ የቁጥጥር ሥርዓትን ማረጋገጥ ይገባል።
በሀገሪቱ ጠንካራ የጤና ቁጥጥር ሥርዓት እንዲኖር የቁጥጥር ተቋማት በሰው ኃይል፣ በአሰራር፣ በቴክኖሎጂና በግብዓት ያላቸውን አቅም ማጎልበትና የተጠሪ ተቋማትን ቅንጅታዊ አሰራር ማጠናከር ይገባል ነው ያሉት።
በተለይም በመድኃኒት አቅርቦት ደህንነት ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴዔታዋ ፥ በዚህ ረገድ የመድኃኒት አቅርቦትን በዲጂታል ሥርዓት ለማስተሳሰር እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡