Fana: At a Speed of Life!

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-

👉 በሀገር ውስጥ የውይይት በር ክፍት ማድረግ አለብን፡፡

👉 ዛሬ ባንዳ የሆነ፥ ከኢትዮጵያ ተቃርኖ የቆመ ሰው ልብ ገዝቶ በቃኝ ካለ ሁሌም ክፍት መሆን አለብን፡፡

👉 በሀገር ጉዳይ ቂም መያያዝ አያስፈልግም፥ ልቤ ታድሷል፣ አእምሮዬ ተቀይሯል ካለ በራችን ክፍት መሆን አለበት፡፡

👉 ይህንንም እያደረግን ቆይተናል፥ ጉዳያችን ኢትዮጵያን የሚጠቅም ከሆነ በይቅርታ ለማለፍ ዝግጁዎች ነን።

👉 በዚህም በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ታጣቂዎች ተመልሰው እየገቡ ይገኛሉ።

👉 ለሰላም ዝግጁ እስከሆነ ድረስ የግል ስሜትን ወደጎን ቶት ለይቅርታ ዝግጁ መሆን ያስፈልጋል።

👉 ብሔራዊ ጥቅም ላይ አሁን ያለው ሁኔታ በጣም ተሻሽሏል።

👉 በተለያዩ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም የተቃረነ እንቅስቃሴን በመቃወም ወደ ሰላም እየመጡ ነው።

👉 በጫካ ሆነው ከመንግስት ጋር ትብብር እያደረጉ የሚገኙት ቁጥራቸው ቀላል የሚባል አይደለም።

በዮናስ ጌትነት

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.