Fana: At a Speed of Life!

ከንቲባ አዳነች አቤቤ 6ኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሥራ አስጀመሩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ 6ኛውን አዲስ መሶብ ዲጂታል አንድ ማዕከል አገልግሎት በጉለሌ ክፍለ ከተማ ስራ አስጀምረዋል ።

ከንቲባዋ በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው እንዳሉት፥ በሀገራዊ ለውጡ የመንግስት የተቋማት ስብራትን በመጠገን ነጻ፣ ገለልተኛ እና የአገልጋይነት መንፈስን የተላበሰ ጠንካራ ተቋማት በመገንባት ስኬታማ ሽግግር ተደርጓል፡፡

የአገልግሎት ዘርፉ ለዘመናት ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትቦ መቆየቱን ጠቅሰው፥ ችግሩን ሥር ነቀል በሆነ መልኩ ለመለወጥ የመሶብ ዲጂታል አንድ ማዕከል ለተገልጋዩ እፎይታን ይዞ መጥቷል ነው ያሉት።

የእነዚህ የለወጥ ፍሬዎች ዋነኛ ተጠቃሚ የሆነው የአዲስ አበባ ህዝብ ማልዶ ወደ አደባባዮች በመውጣት የዘወትር ድጋፉን አጽንቷል ያሉት ከንቲባዋ፥ መንግስት ከህዝቡ ጋር ያሳካው ድል እና የደረሰበት ርቀት ቀላል እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.