Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መቐለ 70 እንደርታን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መቐለ 70 እንደርታን 3 ለ 0 አሸንፏል።

ቀን 9 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደርገው ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የማሸነፊያ ግቦች ሁዘይፋ ሻፊ እና ናትናኤል (2) ከመረብ አሳርፈዋል።

እንዲሁም ቀደም ብሎ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የተደረገው የኢትዮጵያ ቡና እና ሸገር ከተማ ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።

በጨዋታው የኢትዮጵያ ቡናን ግብ አቡበከር አዳሙ ሲያስቆጥር÷ የሸገር ከተማን ደግሞ አሚር አብዶ ከመረብ አሳርፏል።

የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ የተጀመረው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ በቅዱስ ጊዮርጊስ 1 ለ 0 መሪነት የመጀመሪያው አጋማሽ ተጠናቅቋል።

እንዲሁም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ምድረ ገነት ሽረ ከድሬዳዋ ከተማ ጨዋታውን ያደርጋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.