ሀድያ ሆሳዕና አርባ ምንጭ ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሀድያ ሆሳዕና አርባ ምንጭ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡
በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የሀድያ ሆሳዕናን የማሸነፊያ ግብ ሄኖክ አርፍጮ በፍጹም ቅጣት ምት ከመረብ አሳርፏል።
ቀደም ብሎ በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ፋሲል ከነማ ሀዋሳ ከተማን 1 ለ 0 ሲያሸንፍ ነገሌ አርሲ እና ኢትዮጵያ መድን 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል ከ12 ሰዓት ጀምሮ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ እና ወላይታ ድቻ ጨዋታቸውን እያደረጉ ናቸው።