Fana: At a Speed of Life!

ቼልሲ ለኤፍ ኤ ዋንጫ ፍጻሜ ደረሰ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ኤፍ ኤ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ መርሐ ግብር ቼልሲ ሊድስ ዩናይትድን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ቀን 11 ሰዓት ላይ በዌምብሌይ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የቼልሲን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ኢንዞ ፈርናንዴዝ አስቆጥሯል፡፡

ውጤቱን ተከትሎም ቼልሲ ለኤፍ ኤ ዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታ መድረሱን አረጋግጧል፡፡

በፍጻሜ ጨዋታም ቼልሲ ከማንቼስተር ሲቲ ጋር የሚፋለሙ ይሆናል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.