Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ ለኢንተርፕራይዞችና አንቀሳቃሾች የመስሪያ ቦታና ሼዶች ሊተላለፉ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተደራጅተው ስልጠና ለወሰዱ ኢንተርፕራይዞችና አንቀሳቃሾች የመስሪያ ቦታና ሼዶችን ሊያስተላልፍ ነው፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳሉት፥ በዛሬው ዕለት በ11ዱም ክፍለ ከተሞች ለሚገኙ 1ሺህ 278 ኢንተርፕራይዞችና 3ሺህ 889 አንቀሳቃሾች የመስሪያ ቦታ እና ሼዶች ይተላለፋሉ፡፡

የሚሰሩ እጆችን እናበረታታለን ያሉት ከንቲባዋ፥ ኢንተርፕራይዞችና አንቀሳቃሾቹ የስራ እድል እንዲፈጠርላቸው እንደየፍላጐታቸው ተደራጅው ስልጠና መውሰዳቸውን ገልጸዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.