Fana: At a Speed of Life!

የአጀንዳ ማሰባሰብ ሒደቱ ነፃ፣ አካታችና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን ተሰርቷል – ኮሚሽነር መስፍን ዓርአያ (ፕ/ር)

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የአጀንዳ ማሰባሰብ ሒደቱ ነፃ፣ አካታችና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን ተሰርቷል አሉ ኮሚሽነር መስፍን ዓርአያ (ፕ/ር)፡፡

ኮሚሽኑ በምክክር ረቂቅ አጀንዳ ዙሪያ ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ማህበራት ጋር እየመከረ ይገኛል፡፡

ኮሚሽነሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ በዚህ ዓመት በሚካሄደው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ 4 ሺህ ተወካዮች ይሳተፋሉ፡፡

በአጀንዳ ማሰባሰብ ሒደቱ 93 በመቶ የሀገሪቱ ወረዳዎች ተደራሽ ሆነዋል ያሉት ኮሚሽነሩ፥ ሒደቱ ነፃ፣ አካታችና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን መሰራቱን ጠቁመዋል፡፡

በዙፋን አምባቸው

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.