Fana: At a Speed of Life!

ቼልሲ ጣሊያናዊውን ተከላካይ ማርኮ ፓሌስትራን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቼልሲ ጣሊያናዊውን የአታላንታ የክንፍ ተከላካይ ማርኮ ፓሌስትራን አስፈርሟል፡፡

የ21 አመቱ ፓሌስትራ የዣቪ አሎንሶ የመጀመሪያ ፈራሚ በመሆን ስታንፎርድ ብሪጅ የደረሰ ሲሆን፤ በ47 ሚሊየን ፓውንድ የዝውውር ዋጋ ቼልሲን ተቀላቅሏል።

ተጨዋቹ ለስድስት ዓመታት በምዕራብ ለንደኑ ክለብ ለመቆየትም ኮንትራት ፈርሟል፡፡

ባሳለፍነው የውድድር ዓመት በውሰት በካግሊያሪ ያሳለፈው ማርኮ ፓሌስትራ፤ የሴሪ ኤ የዓመቱ ምርጥ ተከላካይ በመሆንም መመረጡ ይታወሳል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.