አርሰናል ክሪስቶስ ሶሊስን ለማስፈረም ተስማማ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሊጉ ሻምፒዮን አርሰናል ክሪስቶስ ሶሊስን ከክለብ ብሩዥ ለማስፈረም ተስማምቷል፡፡
የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ለተጫዋቹ ዝውውር 40 ሚሊየን ዩሮ እንደሚከፍል ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡
የ24 ዓመቱ የፊት መስመር ተጫዋቹ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ለክለብ ብሩዥ ባደረጋቸው 52 ጨዋታዎች 22 ግቦችን አስቆጥሮ 29 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል፡፡