Fana: At a Speed of Life!

ከታሪክ ሳይማሩ በእሳት መጫወት አዙሪት ውስጥ ስለሚከተን ተቀናጅተን እንስራ -ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 15፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በበኒሻንጉል ጉሙዝ መተከል ዞን በንጹሀን ዜጎች ላይ በደረሰው የህይወት ህልፈትና አካል ጉዳት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ።

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ሞትን በፍጹም መላመድ የለብንም ብለዋል።

በመተከል በንጹሃን ዜጎች፥ ሴቶች፥ ሕጻናት እና ቤተሰብ ላይ በየጊዜው የሚፈጸሙ ግድያ በጽኑ የሚወገዝ ነው ማለታቸውን ከፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

ከታሪክ ሳይማሩ በእሳት መጫወት አዙሪት ውስጥ የሚከተን ስለሆነ ተቀናጅተን እንድንሰራ በአደራ ጭምር እጠይቃለሁ ብለዋል።

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል www.youtube.com/fanatelevision ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.