Fana: At a Speed of Life!

“የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል የንቅናቄ ኮንፈረንስ መካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 12 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) “የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል የንቅናቄ ኮንፈረንስ በድሬዳዋና በደቡብ ክልል የተለያዩ ዞኖች መካሄድ ጀምሯል፡፡

መድረኩ የሴቶችን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ በሚደረገው ጉዞ ውስጥ እንቅፋት የሚሆኑ ችግሮችን ነቅሶ በማውጣትና በግልጽ በመነጋገር በየደረጃው ችግሮች እየተፈቱ እንዲሄዱ የሚረዳ እንዲሁም የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትና ፖለቲካዊ ተሳትፎ በመሰረታዊነት ለመመለስ የሚረዳ ነው ተብሏል፡፡

መድረኩ በቀጣዮቹ ቀናትም በመላው ሀገሪቱ እንደሚካሄድ ታውቋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.