Fana: At a Speed of Life!

ለ135 ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ትግራይ ክልል ገብተው የሰብአዊ ድጋፍ ሂደቱን እንዲዘግቡና እንዲያግዙ ፈቃድ ተሰጠ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 17 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በትግራይ ክልል የሰብዓዊ እርዳታ ለማድረግ ላመለከቱ እና ዓለም አቀፍ መመዘኛውን ላሟሉ የ11 ዓለም አቀፍ የሚዲያ አባላትን ጨምሮ ለ135 ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና ሰራተኞች ወደ ትግራይ ክልል በመግባት የሰብዓዊ ድጋፍ ሂደቱን እንዲያግዙ እና እንዲዘግቡ ፈቃድ ተሰጥቷል፡፡

መንግስት ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውና ቀደም ሲል በሴፍቲኔት ፕሮግራም ታቅፈው ድጋፍ ይደረግላቸው የነበሩ 1 ነጥብ 8 ሚሊየን ዜጎችን ጨምሮ የ2 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች ልየታ ተደርጎ እንደነበር የሰላም ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ይሁን እንጅ በማንኛውም ሁኔታ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል የተባሉ ወገኖችን በማካተት ለ3 ነጥብ 1 ሚሊየን ወገኖች ድጋፍ ማድረግ መቻሉንም ነው ያስታወቀው፡፡

ሚኒስቴሩ ለወገኖች ለመድረስ በተደረገው ርብርብ ለማገዝ ለተሳተፉ አካላትም ምስጋናውን አቅርቧል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.