የእርዳታ እህል ይዘው መቀሌ የገቡ የጭነት ተሽከርካሪዎች ቁጥር 277 ደረሰ
አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ተጨማሪ 57 የእርዳታ እህል የጫኑ ተሽከርካሪዎች መቀሌ መግባታቸውን የወቅታዊ ሁኔታ መረጃ ማጣሪ አስታውቋል፡፡
ባሳለፍነውሃምሌ 30 ቀን የእርዳታ እህል ጭነው መቀሌ የገቡ ተሽከርካሪዎች ቁጥር 220 መድረሱ ይታወሳል፡፡
ሰሞኑን ተጨማሪ 57 የእርዳታ እህል የጫኑ ተሽከርካሪዎች መቀሌ መግባታቸውን ተከትሎም አጠቃላይ የእርዳታ እህል ጭነው ስፋራው የደረሱ መኪናዎች ቁጥር 277 ደርሷል፡፡