Fana: At a Speed of Life!

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የተለያዩ ሹመቶችን አጸደቀ

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 15 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት በ2ኛ ቀን ውሎው የተለያዩ ሹመቶችን አጸደቀ።

ምክር ቤቱ በክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የቀረቡ የተለያዩ የስራ ሃላፊዎችን ሹመት አጽድቋል።

በዚህ መሰረት፡-

1ኛ. አቶ ጸጋዬ ማሞ – የመንግሥት ዋና ተጠሪ

2ኛ. አቶ ማስረሻ በላቸው – በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የግብርና ቢሮ ኃላፊ

3ኛ. አቶ አልማው ዘውዴ – በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ

4ኛ. አቶ ሳጂዮ ሳፒ – በመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ

5ኛ. አቶ ተዘራ ወልደማርያም – ረዳት የመንግስት ተጠሪ በመሆን የፖለቲካ እና የርዕዮተ ዓለም ዘርፍ ኃላፊ

6ኛ. አቶ በላይ ተሰማ – የመንግሥት ረዳት ተጠሪ ሆነው የአደረጃጀት ዘርፍ እንዲመሩ ተሹመዋል።

ከዚህ ባለፈም ምክር ቤቱ የካቢኔ አባላትን ሹመት ያፀደቀ ሲሆን :-

1. ኢንጂነር የማታዓለም ቸኮል – የከተማ እና ቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ

2. ወይዘሮ ወሠነች ቶማስ – የፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ

3. ወይዘሮ ፋንታሁን ብላቴ – የባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ

4. አቶ አንድነት አሸናፊ – የሠላም እና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ

5. አቶ አሰፋ ጊንዶ – አርብቶ አደርና ቆላማ አካባቢዎች ቢሮ ኃላፊ

6. አቶ ተክሌ በዛብህ – የፍትህ ቢሮ ኃላፊ

7. አቶ ተመስገን ከበደ – የንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ

8. ኢንጂነር በየነ በላቸው – የውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ

9. አቶ ተስፋዬ እንዳሻው – የክህሎት እና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ

10. አቶ ኢብራሂም ተማሚ – የጤና ቢሮ ኃላፊ

11. ወይዘሮ ገነት መኩሪያ – የሴቶች፣ ህጻናት እና ወጣቶች ቢሮ ኃላፊ

12. አቶ ግዛው ጋጊያ – የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ

13. አቶ የሺዋስ ዓለሙ – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ

14. ወይዘሮ ሕይወት አሰግድ – የገቢዎች ቢሮ ኃላፊ

15. አቶ አስራት ሀዳሮ – ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ

16. ዶክተር ኢንጂነር አስራት ገብረማርያም – የደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ለውጥ ቢሮ ኃላፊ

17. ወይዘሮ ቤተልሔም ልዑል – የኢንተርፕራይዝ እና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሆነው በሙሉ ድምጽ መሾማቸውን ከደሬቴድ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.