ኢትዮጵያና እስራኤል በኢንቨስትመንት የድጋፍ ስራዎችን በጋራ መስራት በሚቻልበት አግባብ ላይ ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ህዳር 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢንቨስትመንት ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜና ምክትል ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን በኢትዮጵያ ከእስራኤል አምባሳደር አለልኝ አድማሱ ጋር ተወያዩ፡፡
በውይይቱ የሁለቱን አገራት የቆየ የኢንቨስትመንት ግንኙነት አጠናክሮ ስለመቀጠል፣ በጋራ የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት አማራጮች ለእስራኤል ባለሀብቶች ማስተዋወቅ በሚቻልበት አግባብ ላይ መክረዋል።
ከዚህ ባለፈም በኢንቨስትመንት ዘርፉ የድጋፍ እና ክትትል ስራዎችን በጋራ መስራት እንዲሁም የአቅም ግንባታ ስራዎች ላይ መሳተፍ በቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ከኢንቨስትመንት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!