ጠመንጃ ያዥ አካባቢ የተለያዩ መሣሪያዎች ትቦ ዉስጥ ተጥለው ተገኙ
አዲስ አበባ፣ ህዳር 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ልዩ ቦታዉ ጠመንጃ ያዥ አካባቢ የተለያዩ መሣሪያዎች ትቦ ዉስጥ ተጥለው ተገኝተዋል።
ፖሊስ ኅብረተሰቡ አካባቢውን በንቃት እንዲቃኝና የተለየ ነገር ሲመለከት ለፖሊስ እንዲያመለክት አሳስቧል።
በዚህም ፡-
1) ታጣፊ ከላሽ ብዛት 1 የውግ ቁጥር 24096 የጥይት ብዛት 114 እና 4 ካዝና
2) ማካሮፍ ሽጉጥ ብዛት 1 የውግ ቁጥሩ የማይታይ የጥይት ብዛት 7 ፍሬ
3) አንድ የአፋር ግሌ የሚመስል ሳንጃ ሲሆን በቀን 17/03/2014 ዓ/ም ተይዞ ለፖሊስ ጣቢያ ገቢ ሆኗል።
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!