Fana: At a Speed of Life!

በአብሮነት፣ በሀይማኖትና ብዝሃነት ላይ ያተኮረ ምክክር በሀረር ከተማ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሰላም በአብሮነት፣ በሀይማኖትና ብዝሃነት ላይ ያተኮረ ምክክር የኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ በሀረር ከተማ እያካሄደ ይገኛል። በመድረኩ ላይ በእንግድነት የተገኙት የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ የምክክር መድረኩ በሀረር…

በገበታ ለሀገር ሦስት ፕሮጀክት ያሉበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 7፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በገበታ ለሀገር ሦስት ፕሮጀክት ማለትም በኮይሻ፣በጎርጎራ እና በወንጪ በቀረቡ ዲዛይን ስራዎች ላይ ያለበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡ በውይይቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ ፕሮጀክቶች የሚከናወኑባቸው ክልሎች ርእሰ መስተዳድሮች፣…

በ782 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 7 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ከሕወሓት ቡድን ጋር በመቀናጀት ግጭቶች ሲያስነሱ፣ ግድያ እና ዝርፊያ ሲፈጽሙ የነበሩ 782 የኦነግ ሸኔ የጥፋት ኃይሎች ላይ እርምጃ መወሰዱን የኦሮሚያ ክልል መንግስት አስታወቀ፡፡ የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ…

አየር መንገዱ ኮቪድ-19 ያስከተለውን ተፅእኖ ተቋቁሞ በማለፍ ከኤርባስ ሽልማት ተበረከተለት

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኮቪድ-19 ያስከተለውን ተፅእኖ ተቋቁሞ በማለፍ ከኤርባስ አውሮፕላን አምራች ኩባንያ ሽልማት ተበከተለት። አየር መንገዱ በአቪዬሽኑ መስክ ላስመዘገበው ስኬት እና ሙያዊ ብቃት እውቅና እና ሽልማቱ እንደተሰጠው ከአየር መንገዱ…

በደቡብ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እየተሰጠ ነው

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 7 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ክልል ሁሉም ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች የ2012 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ዛሬ መሰጠት ጀመረ፡፡ ለሁለት ቀናት የሚቆየው ፈተና በ3 ሺህ 782 የፈተና ጣቢያዎች እየተሰጠ ይገኛል፡፡ 292 ሺህ 769 ተማሪዎችም ፈተናውን እየወሰዱ…

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር  ፍቅረስላሴ ወግደረስ የቀብር ስነ ስርዓት ተፈፀመ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በደርግ ዘመነ መንግስት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት ፍቅረስላሴ ወግደረስ የቀብር ስነ ስርዓት ተፈፀመ። የቀብር ስነ ስርዓታቸው በመንበረ ፀባኦት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት ተፈፅሟል። የቀድሞው ጠቅላይ…

በ1 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ወጪ እየተገነባ የሚገኘው የደብረብርሃን አንኮበር የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት እየተፋጠነ ነው

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) 42 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የደብረ ብርሃን አንኮበር የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ። በመንገድ ፕሮጀክቱ የስራ እንቅስቃሴ የአፈር ሙሌትና፣ ድልዳሎ፣ የውሃ መፋሰሻ ቱቦ ቀበራ የሰብ ቤዝ ስራ…

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ተወካዮች በድሬዳዋ ከሚኖሩ የክልሉ ተወላጆች ጋር እየተወያዩ ነው

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 7 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ተወካዮች በድሬዳዋ ከሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጆች ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ እየተወያዩ ነው። የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አስተባባሪ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የአዲስ አበባ ከተማ የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ…

ደራሲ እና ተዋናይ ተባባሪ ፕሮፌሰር ተስፋዬ ገሰሰ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ደራሲ እና ተዋናይ ተባባሪ ፕሮፌሰር ተስፋዬ ገሰሰ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ተባባሪ ፕሮፌሰር ተስፋዬ የተለያዩ መፅሃፍትን የደረሱ ሲሆን በተለያዩ ፊልሞች እና ድራማዎች ላይም በተዋናይነት ተሳትፈዋል። ብሄራዊ ቴዓትር ቤት የሽኝት ፕሮግራም…

በአካባቢ ላይ የድምፅ ብክለት ያደረሱ 11 መጠጥ ቤቶች እና ሬስቶራንቶች ታሸጉ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 7፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ በአካባቢ ላይ የድምፅ ብክለት ያደረሱ 11 መጠጥ ቤቶች እና ሬስቶራንቶች መታሸጋቸው ተገለጸ፡፡ ከ100 በላይ መጠጥ ቤቶች ላይ የአካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን የአካባቢ ብክለት ቁጥጥር ባለሙያዎች ባደረጉት የድምፅ ልኬት…