Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ኤደን ሀዛርድ ከቤልጂየም ብሔራዊ ቡድን ራሱን አገለለ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አሁን በሪያል ማድሪድ እየተጫወተ የሚገኘው ኤደን ሀዛርድ ከቤልጂየም ብሔራዊ ቡድን ራሱን ማግለሉን ይፋ አድርጓል፡፡ ቤልጂየም በጊዜ ከዓለም ዋንጫው መሰናበቷን ተከትሎ ነው ኤደን ሀዛርድ ከብሔራዊ ቡድኑ ራሱን ያገለለው፡፡ የ31 ዓመቱ ሀዛርድ ለሀገሩ በ126 ጨዋታዎች ተሰልፎ 33 ጎሎችን ማስቆጠሩን ጎል ዶት ኮም ዘግቧል፡፡ የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ቀደም ሲል ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸው ይታወሳል፡፡
Read More...

የክርስቲያኖ ሮናልዶ ቋሚ አሰላለፍ ውስጥ አለመግባት አዳዲስ የፖርቹጋል ኮከቦችን አስተዋውቋል

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በስዊዘርላንዱ ጨዋታ የክርስቲያኖ ሮናልዶ ቋሚ አሰላለፍ ውስጥ አለመግባቱ አዳዲስ የፖርቹጋል ኮከቦች በመድረኩ እንዲታወቁ እድል ሰጥቷል፡፡ ትላንት ምሽት ፖርቹጋል ስዊዘርላንድን 6 ለ 1 ባሸነፈችበት ጨዋታ አሰልጣኝ ፈርናንዶ ሳንቶስ ክርስቲያኖ ሮናልዶን ተጠባባቂ ወንበር ላይ በማስቀመጥ በምትኩ የቤኔፊካውን አጥቂ ጎንዛሎ ራሞስን…

ፖርቹጋል ስዊዘርላንድን በሰፊ ውጤት በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ፖርቹጋል ስዊዘርላንድን በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች። ምሽት አራት ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ ፖርቹጋል ስዊዘርላንድን 6ለ 1 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፋለች። ለፖርቹጋል ጎንሳሎ ራሞሰ በ17ኛው ፡ በ51ኛውና በ67ኛው ደቂቃዎች ላይ ባስቆጠራቸው ጎሎች ሃትሪክ ሲሰራ ቀሪዎቹን ሶስት ጎሎች ደግሞ ፔፔ በ33ኛው ፥ ራፋኤል…

ሞሮኮ ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀለች ብቸኛዋ አፍሪካዊት ሀገር ሆነች

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 27 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታሩ ዓለም ዋንጫ ሞሮኮ ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀለች ብቸኛዋ አፍሪካዊት ሀገር ሆናለች፡፡ ሞሮኮ ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀለች ብቸኛዋ አፍሪካዊት ሀገር ሆነች አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 27 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታሩ ዓለም ዋንጫ ሞሮኮ ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀለች ብቸኛዋ አፍሪካዊት ሀገር ሆናለች፡፡ በዓለም ዋንጫው የጥሎ…

በፕሪሚየር ሊጉ አዳማ ከተማ ተጋጣሚውን ረታ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አዳማ ከተማ ለገጣፎ ለገዳዲን 3 ለ0 አሸነፈ፡፡ የአዳማ ከተማን የማሸነፊያ ጎሎች አቡበከር ወንድሙ በ14ኛው እና አሜ መሐመድ በ72ኛውና በ73ኛው ደቂቃ አስቆጥረዋል፡፡ በድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም እየተካሔደ የሚገኘው የ11ኛ ሣምንት ጨዋታ መርሐ ግብር ሲቀጥል÷ ምሽት 1 ሰዓት ላይ…

በጥሎ ማለፉ ሞሮኮ ከስፔን እንዲሁም ፖርቹጋል ከስዊዘርላንድ ዛሬ ይጫወታሉ

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 27 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታሩ ዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይካሄዳሉ። በዛሬው የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ማምሻውን 12 ሰዓት ላይ በሚካሄድ ጨዋታ አፍሪካዊቷ ሞሮኮ ከስፔን ይገናኛሉ። በሌላ ጨዋታ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ፖርቹጋል ከስዊዘርላንድ ጋር የምታደርገው ጨዋታም ከወዲሁ ተጠባቂ ሆኗል። ትናንት በተካሄደ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ…

ብራዚል ደቡብ ኮሪያን 4 ለ 1 በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታር ዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ብራዚል እና ደቡብ ኮሪያ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን አካሂደዋል፡፡ በዚህም የአምስት ጊዜ የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮኗ ብራዚል ደቡብ ኮሪያን 4 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች፡፡ የብራዚልን የማሸነፊ ግቦች ቪኒሺየስ ጁኒየር፣ ኔይማር…