Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

አዝናኙ የካሜሩን እና የሰርቢያ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ድራማዊ ትዕይንት ያስተናገደው የካሜሩን እና የሰርቢያ ጨዋታ 3 አቻ ተጠናቋል፡፡ በጨዋታው ካሜሩን በሰርቢያ ብልጫ ተወስዶባት 3 ለ 1 ስትመራ ብትቆይም በቪንሰንት አቡበከር እና ቺፖ ሞቲንግ ሁለት ጎሎች ታግዛ አቻ መሆን ችላለች። የካሜሩንን ጎሎች ጄን ካሴሌቶ፣ ቪንሰንት አቡበከር እና ቺፖ ሞቲንግ ሲያስቆጥሩ የሰርቢያን ጎሎች ደግሞ ስትራኒያ ፓቭሎቪች፣ ሳቪች እና አሌክሳንደር ሚትሮቪች አስቆጥረዋል፡፡ ከጨዋታው ቀደም ብሎ ለኢንተር ሚላን የሚጫወተው ግብ ጠባቂው አንድሬ ኦናና ከአሰልጣኙ ጋር…
Read More...

የሊጉ መርሐ ግብሮች እና ተስተካካይ ጨዋታዎች በድሬዳዋ መካሄዳቸውን ይቀጥላሉ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከ11ኛ እስከ 13ኛ ሳምንት ያሉ ጨዋታዎችን ጨምሮ ተስተካካይ ጨዋታዎች በድሬዳዋ መካሄዳቸውን ይቀጥላሉ፡፡ የ2015 ዓ.ም ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከ1ኛ እስከ 5ኛ ሳምንት በባህር ዳር ከተማ የተከናወነ ሲሆን ከ6ኛ እስከ 10ኛ ሳምንት ያሉ ጨዋታዎች በድሬደዋ ከተማ እየተካሄደ…

በዛሬው የዓለም ዋንጫ ሁለት የአፍሪካ ሀገራት የሚሳተፉበትን ጨምሮ አራት ጨዋታዎች ይካሔዳሉ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዘጠነኛ ቀኑን በያዘው የኳታሩ የዓለም ዋንጫ ውሎ ካሜሮን እና ጋና የሚሳተፉበትን ጨምሮ አራት ጨዋታዎች ይከናወናሉ፡፡ በዚሁ መሰረት በምድብ ሰባት የተደለደሉት አፍሪካዊቷ ካሜሮን እና ሰርቢያ ቀን ሰባት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ፡፡ በዚሁ ምድብ የተደለደሉት ብራዚል እና ስዊዘርላንድ ደግሞ ምሽት አንድ ሰዓት ላይ…

ስፔንና ጀርመን አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) - የምድባቸውን ሁለተኛ ጨዋታ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ያደረጉት ስፔንና ጀርመን ሳይሸናነፉ ቀርተዋል። ሁለቱ ቡድኖች 90 ደቂቃውን 1ለ1 በሆነ ውጤት አጠናቀዋል። ውጤቱን ተከትሎ ጀርመን በአንድ ነጠብ በምድቧ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች። ስፔን በአንፃሩ በ4 ነጥብ ምድቡን አየመራች ትገኛለች። በዚህ ምድብ ሚገኙት…

ካናዳ ከኳታሩ የዓለም ዋንጫ ተሰናበተች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታሩ የዓለም ዋንጫ ካናዳ በክሮሺያ 4 ለ 1 መሸነፏን ተከትሎ ከውድድሩ ሁለተኛዋ ተሰናባች ሀገር ሆናለች። የካናዳው አልፎንሶ ዴቪስ በዛሬው ጨዋታ ክሮሺያ ላይ በ2ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ጎል በኳታሩ የዓለም ዋንጫ ፈጣኗ ጎል ሆና ተመዝግባለች። ከዚህ ቀደም የኔዘርላንድሱ ኮዲ ጋክፖ በ6ኛው ደቂቃ የውድድሩን ፈጣን ጎል…

ተጠባቂው የስፔን እና ጀርመን ጨዋታ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ ምሽት ስፔን ከጀርመን የሚያደርጉት የዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታ በጉጉት ይጠበቃል፡፡ በምድብ አምስት የተደለደሉት ሁለቱ ሀገራት ከምድብ ለማለፍ ምሽት 4 ሰዓት በኳታሩ አል ባይት ስታዲየም ፍልሚያቸውን ለማድረግ ቀጠሮ ይዘዋል፡፡ ኮስታሪካን በሰፊ ውጤት ያሸነፈችው ስፔን በጊዜ ከምድቡ ለማለፍ ጨዋታዋን የምታደርግ ሲሆን÷…

በዓለም ዋንጫ አፍሪካዊቷ ሞሮኮ ወሳኝ የምድብ ድሏን አስመዘገበች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዓለም ዋንጫ አፍሪካዊቷ ሞሮኮ ቤልጂየምን 2 ለ 0 በማሸነፍ የመጀመሪያ ድሏን አስመዝግባለች፡፡ በጨዋታው ብርቱ ተፎካካሪ ሆና የቀረበችው የሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር ሞሮኮ ከእረፍት መልስ አብዱልሃሚድ ሳብሪል እና ዛካሪያ አቡክላል ባስቆጠሯቸው ጎሎች ቤልጂየምን በማሸነፍ ወሳኝ ድል አስመዝግባለች፡፡ ሞሮኮ ከሴኔጋል በመቀጠል…