Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

በዓለም ዋንጫ አፍሪካዊቷ ሴኔጋል ኳታርን 3ለ1 አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዓለም ዋንጫ የምድብ 2 የሁለተኛ ዙር ጨዋታ  አፍሪካዊቷ ሴኔጋል  አዘጋጇን ሀገር ኳታር  3 ለ 1 አሸንፋለች፡፡ በኳታር አልቱማም ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቡሊያን ዲያ፣ ፋሙራ ዴዴሁ እና ባባ ዲየንግ  የሴነጋልን ጎሎች ሲያስቆጥሩ ሞሃመድ ሞንታሪ የኳታርን ብቸኛ ጎል አስቆጥሯል፡፡ የቴራንጋ አንበሶቹ በኔዘርላንድስ ከደረሰባቸው ሽንፈት በማገገም ከምድቡ ለማለፍ  እና በኳታር ለመቆየት የሚያስችላቸውን ድል አስመዘግበዋል፡፡ የአፍሪካ ሻምፒዮኖቹ በመጀመሪያው ዙር የአለም ዋንጫ ጨዋታ…
Read More...

በዓለም ዋንጫው የምድብ ሁለተኛ ጨዋታዎች ዛሬ ይጀምራሉ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ አፍሪካዊቷ ሴኔጋል የምትሳተፍበትን ጨምሮ አራት የምድብ ሁለተኛ ጨዋታዎች ይከናወናሉ፡፡ በዚህም በምድብ ሁለት የተደለደሉት ዌልስ ከኢራን ቀትር 7 ሰዓት ላይ የሚጫወቱ ሲሆን ÷ በተመሳሳይ በዚሁ ምድብ የሚገኙት እንግሊዝ ከአሜሪካ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያካሂዳሉ፡፡ በሌላ የጨዋታ መርሐ ግብር በምድብ አንድ…

በዓለም ዋንጫ ጨዋታ ፖርቹጋል ጋናን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸነፈች

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 15 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ22ኛው የኳታር ዓለም ዋንጫ ጨዋታ የአምስተኛ ቀን ውሎ በምድብ ስምንት በተደረገ ጨዋታ ፖርቹጋል ጋናን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡ የፖርቹጋልን የመጀመሪያ ግብ ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በፍጹም ቅጣት ምት በ65 ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡ ጃኦ ፍሊክስ እና ራፋይል ሌዮ ደግሞ 78 ኛው እና 80ኛው ደቂቃ ላይ የፖርቹጋልን…

በዓለም ዋንጫ ጨዋታ ስዊዘርላንድ ካሜሮንን 1 ለ 0 አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ህዳር 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሌላኛዋ የአፍሪካ ተወካይ ካሜሮን በኳታር የዓለም ዋንጫ ጨዋታ በሀገሯ ልጅ በተቆጠረባት ግብ በስዊዘርላንድ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች፡፡ በጨዋታው ብሪል ኤምቦሎ ከሽኮርዳን ሻኪሪ የተሻገረለትን ኳስ ወደ ግብ ቀይሮ ስዊዘርላንድ የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋን እንድታሸንፍ አድርጓል፡፡ በትውልድ ካሜሮናዊ በዜግነት…

በዛሬው የዓለም ዋንጫ ሁለት የአፍሪካ ሀገራት የሚሳተፉበትን ጨምሮ አራት ጨዋታዎች ይካሔዳሉ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አምስተኛ ቀኑን በያዘው የዓለም ዋንጫ ውሎ ካሜሮን እና ጋና የሚሳተፉበትን ጨምሮ አራት ጨዋታዎች ይከናወናሉ፡፡ በዚሁ መሰረት በምድብ ሰባት የተደለደሉት አፍሪካዊቷ ካሜሮን ከስዊዘርላንድ ቀን ሰባት ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ፡፡ በዚሁ ምድብ የተደለደሉት ብራዚል እና ሰርቢያ ምሽት አራት ሰዓት ላይ…

ስፔን ኮስታሪካን ከግማሽ ደርዘን ጎል በላይ በማስቆጠር አሸነፈች

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 14 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዓለም ዋንጫው አራተኛ ቀን ውሎ ስፔን ከግማሽ ደርዘን ጎል በላይ በማስቆጠር አሸንፋለች። በምድብ 5 የተደለደለችው ስፔን የደቡብ አሜሪካዋን ኮስታሪካን 7 ለ 0 በሆነ ሰፊ የጎል ልዩነት ማሸነፍ ችላለች። ዳኒ ኦልሞ፣ ማርኮ አሴንሲዮ፣ ጋቪ፣ ካርሎስ ሶለር እና አልቫሮ ሞራታ አንድ አንድ ጎሎችን ሲያስቆጥሩ ፌራን ቶሬስ…

በዓለም ዋንጫ ጨዋታ ጃፓን ጀርመንን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸነፈች

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 14 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ22ኛው ዓለም ዋንጫ የአራተኛ ቀን ውሎ በምድብ አምስት በተደረገ ጨዋታ ጃፓን ጀርመንን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡ የማንችስተር ሲቲው የአማካይ ክፍል ተጫዋች ኢልካይ ጉንዶጋን በ33ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠረው ግብ የጀርመን ብሔራዊ ቡድንን መሪ ማድረግ ችሎ ነበር። ይሁንና ተቀይሮ የገባው የጀርመኑ…