Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ዋልያዎቹ በቀጣይ ሳምንት ከዛምቢያ ጋር የወዳጅነት ጨዋታ ያደርጋሉ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ወንዶች ብሄራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) በቀጣይ ሳምንት ከዛምቢያ አቻው ጋር የወዳጅነት ጨዋታ እንደሚያደርጉ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ።   የወዳጅነት ጨዋታው ጥቅምት 12ና 15 ቀን 2013 በአዲስ አበባ ስታድየም እንደሚካሄድ ነው የተገለፀው።   ብሄራዊ ቡድኑ ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ዝግጅቱን በካፍ አካዳሚ እያከናወነ የሚገኘ ሲሆን ከኒጀር ጋር ከሚያደርገው የደርሶ መልስ ጨዋታ በፊት ነው የወዳጅነት ጨዋታውን የሚያከናውነው።
Read More...

የኮማንደር አሰልጣኝ ሁሴን ሽቦ “አዳኙ አሰልጣኝ” መጽሃፍ ተመረቀ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኮማንደር አሰልጣኝ ሁሴን ሽቦ "አዳኙ አሰልጣኝ" መጽሃፍ በዛሬው እለት ተመርቋል። በመጽሃፉ ምረቃ ላይም የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ኃላፊዎች ተገኝተዋል።…

በፖላንድ የዓለም የግማሽ ማራቶን ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶችም በሴቶችም 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቁ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በፖላንድ ጊዲኒያ የዓለም የግማሽ ማራቶን ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶችም በሴቶችም 3ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል። በወንዶች በተካሄደው የዓለም የግማሽ ማራቶን ሻምፒዮና ኢትዮጵያው አትሌት አምደወርቅ ዋለልኝ 59 ደቂቃ 08 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመግባት 3ኛ ደረጃ ይዞ ውድድሩን ማጠናቀቅ ችሏል።…

በስፖርት አመራርነት የሚታወቁት አቶ ያሚ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ ውስጥ በስፖርት አመራርነት እጅግ ከፍተኛ ሚና የነበራቸው አቶ ያሚ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡   አቶ ያሚ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በተወለዱ በ66 ዓመታቸው በትናንትናው ዕለት ነው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት፡፡   አቶ ያሚ ስራ ከጀመሩበት…

የጃፓኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀገራቸው የ2021 ኦሊምፒክን እንደምታስተናግድ ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጃፓኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ዮሺዴ ሱጋ ሀገራቸው የ2021ዱን ኦሊምፒክ እንደምታስተናግድ ቃል ገብተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዮሺዴ ሱጋ ከዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ ጋር በመስራት ዕውን ይሆናል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማንኛውንም ጥረት አድርገን ኦሊምፒኩን እናስተናግዳለን ብለዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዮሺዴ…

ትውልደ ኢትዮጵያዊው አዶናይ ለማንቼስተር ዩናይትድ ፈረመ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 4፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ትውልደ ኢትዮጵያዊው ታዳጊ አዶናይ ወንድወሰን ለማንቼስተር ዩናይትድ ፈረመ፡፡ በዜግነት እንግሊዛዊ የሆነው የ16 ዓመቱ አዶናይ ከክለቡ ጋር ለሦስት ዓመታት የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል፡፡ በግራ መስመር ቦታ ላይ የሚጫወተው አዶናይ በተለያዩ ክለቦች ውስጥ ትኩረት አግኝቶ እንደነበርም ነው የተገለጸው፡፡ ላለፉት ሁለት…