ስፓርት
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ክብረ ወሰን በመስበር አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያዊው አትሌት ዳዊት ወልዴ እና አትሌት ሩቲ አጋ በ2025 የሺያሚን የማራቶን ሩጫ ውድድር ሪከርድ በመስበር አሸንፈዋል፡፡
በዢያሜን ማራቶን 2025 የወንዶች ሩጫ ውድድር አትሌት ዳዊት ወልዴ 2:06:06 በሆነ ሰዓት በመግባት ቀደም ሲል የተያዘውን ክብረ ወሰን በመስበር አሸንፏል፡፡
ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት አሰፋ ቦኪ ደግሞ ውድድሩን በ2፡06፡32 በማጠናቀቅ 3ኛ ደረጃን ይዟል፡፡
በዚሁ ውድድር በሴቶች አትሌት ሩቲ አጋ ሶራ ውድድሩን 2፡18፡46 በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ…
Read More...
ባሕርዳር ከተማና ድሬዳዋ ከተማ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ12ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ባሕርዳር ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ ባሕርዳር ከተማ ሙጂብ ቃሲም ባስቆጠራት ግብ እስከ ጨዋታው መጠናቀቂያ ድረስ መምራት ችሎ ነበር፡፡
ይሁን እንጂ አሕመድ ረሺድ 88ኛው ደቂቃ ላይ ኳስ…
ማንቼስተር ሲቲ በሰፊ የግብ ልዩነት ሲያሸንፍ ቼልሲ ነጥብ ጥሏል
አዲስ አበባ፣ ታህሣሥ 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ20ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ-ግብር ማንቼስተር ሲቲ ዌስትሃም ዩናይትድን 4 ለ 1 ሲያሸንፍ ቼልሲ ከክሪስታል ፓላስ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ ለማንቼስተር ሲቲ የማሸነፊያ ግቦቹን ኩፋል በራሱ ግብ ላይ እንዲሁም ኧርሊንግ ሃላንድ (2) እና ፊል ፎደን ሲያስቆጥሩ÷…
የኢትዮጵያ ክለቦች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ለተከታታይ አምስት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ ክለቦች የአጭር፣ መካከለኛ፣ የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ርምጃ እና የሜዳ ተግባራት አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጠናቋል፡፡
ሻምፒዮናውን በሴትም በወንደም ድምር ውጤት የኢትዮጵያ ንግድ 319 ዋንጨዋችን በመሰብሰብ በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ፣ መቻል 315 ዋንጫዎችን…
ቶተንሃም ሆትስፐር በሜዳው በኒውካስል ዩናይትድ ተሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ20ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ መርሐ-ግብር ቶተንሃም ሆትስፐር በሜዳው በኒውካስል ዩናይትድ 2 ለ 1 ተሸንፏል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ከ30 በቶተንሃም ሆትስፐር ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የኒውካስልን የማሸነፊያ ግቦች አንቶኒ ጎረድን እና አሌክሳንደር አይሳክ ሲያስቆጥሩ ዶሚኒክ ሶላንኬ የቶተንሃምን ማስተዛዘኛ ግብ…
አርሰናል ብሬንትፎርድን በሜዳው አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 23፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ19ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ወደ ጌቴክ ኮሚኒቲ ስታዲየም ያቀኑት መድፈኞቹ ብሬንትፎርድን 3 ለ 1 አሸንፈዋል፡፡
ምንም እንኳን ንቦቹ በብሪያን ሙቤሞ ግብ ሲመሩ ቢቆዩም÷ ጋብሬል ጀሱስ፣ ሚኬል ሜሪኖ እና ጋብሬል ማርቲኔሊ ለመድፈኞቹ ባስቆጠሯቸው ጎሎች 3 ለ 1 ተረትተዋል፡፡
39 ነጥቦችን የሰበሰበው…
የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን የዓመቱ ምርጥ ቡድን ሽልማትን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 23፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን የዓለም አቀፉ የስፖርት ፕሬስ ማህበር (ኤአይፒኤስ) የ2024 የዓመቱ ምርጥ ቡድን ሽልማትን አሸነፈ፡፡
ብሔራዊ ቡድኑ በ111 ሀገራት ከሚገኙ 518 ጋዜጠኞች በተሰበሰብ ድምፅ በአጠቃላይ 579 ነጥቦችን በማግኘት ሽልማቱን አሸንፏል።
የዩሮ 2024 አሸናፊው የስፔን ብሔራዊ ቡድን 552 ድምፆችን…