Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

የቀድሞው የስፔን እግር ኳስ ማህበር ፕሬዚዳንት የሶስት አመት ዕግድ ተላለፈባቸው

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 19 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ አስተዳዳሪ አካል (ፊፋ) በቀድሞው የስፔን እግር ኳስ ማህበር ፕሬዚዳንት ሉዊስ ሩቢያሌስ ላይ ዕገዳ አስተላለፈ። ፊፋ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ከማንኛውም ስፖርታዊ ጉዳዮች ለሶስት አመታት እንዲታገዱ ነው ውሳኔ ያሳለፈው። ሩቢያሌስ ስፔን አሸናፊ በሆነችበት የሴቶች የዓለም ዋንጫ የሽልማት ሥነ ሥርአት ላይ የቡድኑን አጥቂ ሄኒ ሄርሞሶን ከንፈር በመሳማቸው ምክንያት በፊፋ በጊዜያዊት ታግደው ጉዳያቸው ሲታይ ቆይቶ ነበር። ከፊፋ ዕግድ በኋላም ባለፈው መስከረም ወር…
Read More...

አትሌት ደሬሳ ገለታ በቤጂንግ ማራቶን ውድድር አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ደሬሳ ገለታ እና አትሌት ይሁንልኝ አዳነ በቤጂንግ 2023 ማራቶን ውደድር አሸንፈዋል፡፡ አትሌት ደሬሳ ገለታ ርቀቱን 2 ሰዓት 7 ደቂቃ ከ41 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ቀዳሚ መሆን ችሏል፡፡ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ይሁንልኝ አዳነ ደግሞ ርቀቱን 2 ሰዓት 7 ደቂቃ ከ42 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመጨረስ…

ሱፐር ሰንዴይ ማንቹሪያን ደርቢ በኦልድትራፎርድ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ10ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ ማንቼስተር ዩናይትድ ከማንቼስተር ሲቲ የሚያደርጉት የማንቹሪያ ደርቢ ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡ ምሽት 12:30 ላይ በሚደረገው ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ከመሪው ቶተንሃም ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ለማጥበብ ወደ ሜዳ የሚገባ ሲሆን ማንቼስተር ዩናትድ ባንፃሩ የደርቢ ክብሩን ለማስጠበቅ እና…

ፋሲል ከነማ ኢትዮጵያ ቡናን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ፋሲል ከነማ ኢትዮጵያ ቡናን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም እየተካሄደ በሚገኘው የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 4ኛ ሳምንት ጨዋታ ፋሲል ከነማ እና ኢትዮጵያ ቡና ተገናኝተዋል፡፡ ፋሲል ከነማ በሁለተኛው የጨዋታ አጋማሽ አማኑኤል…

የአራተኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀቁ

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 16 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አራተኛ ሳምንት ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ተካሂደዋል። 9 ሰአት ላይ በተደረገ ጨዋታ ሀምበርቾ ከሀድያ ሆሳዕና ያደረጉት ጨዋታ ያለምንም ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል። ምሽት 12 ሰአት ላይ በተደረገ ጨዋታ ደግሞ የአምናው ሻምፒዮን ቅዱስ ጊዮርጊስ ከአዳማ ከተማ ተገናኝተዋል። ጨዋታውን አዳማ ከተማ…

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጣና ሞገዶቹ ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአራተኛ ሣምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ባሕርዳር ከተማ ወልቂጤ ከተማን 3 ለ 0 አሸንፏል፡፡ 12፡00 ላይ በአዳማ ሣይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በተደረገው ጨዋታ÷ ሀብታሙ ታደሰ የባሕርዳር ከተማን ሦስት ጎሎች በማስቆጠር ሃትሪክ ሠርቷል፡፡ ሃትሪኩም እስካሁን ባለው የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ውድድር…

ሳንድሮ ቶናሊ ለ10 ወራት ከእግርኳስ ታገደ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኒውካስል ዩናይትዱ የመሀል ክፍል ተጫዋች ሳንድሮ ቶናሊ ከስፖርት ውርርድ ጋር በተያያዘ ለ10 ወራት ከእግርኳስ መታገዱን የጣሊያን እግኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡ ወጣቱ ጣሊያናዊ ኤሲ ሚላን በነበረበት ወቅት ህገ ወጥ የእግርኳስ ደህረ ገፆችን በመጠቀም የእግር ኳስ ውርርድ ማድረጉ በመረጋገጡ ነው ውሳኔው የተላለፈበት፡፡…