ስፓርት
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ቼልሲ፣ ማንቼስተር ሲቲ እና አስቶንቪላ አሸንፈዋል
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ20ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ቼልሲ፣ ማንቼስተር ሲቲ እና አስቶንቪላ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡
9፡30 ከሜዳው ውጭ ሉተን ታውንን የገጠመው ቼልሲ 3 ለ 2 አሸንፏል፡፡
ኑኖ ማዱዌኬ እና ኮል ፓልመር (ሁለት) የቼልሲን ጎሎች ሲያስቆጥሩ ኤሊያህ አደባዮ እና ሮዝ ባርክሌይ የሉተንን ሁለት ጎሎች አስቆጥረዋል፡፡
እንዲሁም 12፡00 ላይ በተደረጉ ጨዋታዎች ማንቼስተር ሲቲ በሮድሪ እና ጁሊያን አልቫሬዝ ሁለት ጎሎች ሼፊልድ ዩናይትድን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ውጤቱን ተከትሎም…
Read More...
በአዲስ አበባ ደርቢ ቡናማዎቹ ተጋጣሚያቸውን አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ደርቢ ኢትዮጵያ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 በማሸነፍ ወሳኝ ሦስት ነጥብ አሳክቷል፡፡
9፡00 ላይ በተደረገው ተስተካካይ ጨዋታ የቡናማዎቹን ብቸኛ ጎል ጫላ ተሺታ ከመረብ አሳርፏል፡፡
በጨዋታው ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ ለመጋራት በተደጋጋሚ ያደረገውን ሙከራ ወደ ውጤት መቀየር ሳይችል ቀርቷል፡፡
ውጤቱን…
አንድሬ ኦናና በካሜሩን ብሔራዊ ቡድን ውስጥ ተካተተ
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የማንቼስተር ዩናይትድ ግብ ጠባቂ አንድሬ ኦናና በኮትዲቯሩ የአፍሪካ ዋንጫ በሚሳተፈው የካሜሩን ብሔራዊ ቡድን ዝርዝር ውስጥ ተካትቷል፡፡
ኦናና በኳታሩ የዓለም ዋንጫ ሀገሩ ከአሰልጣኝ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት በጊዜያዊነት ከብሔራዊ ቡድኑ ርቆ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
ካሜሩን በአጠቃላይ 27 ተጫዋቾችን ይፋ ያደረገች ሲሆን÷…
ተጠባቂው የሸገር ደርቢ በነገው ዕለት ይካሄዳል
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሁለቱን የሸገር ክለቦች ኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስን የሚያገናኘው የሸገር ደርቢ ጨዋታ በነገው ዕለት ይካሄዳል፡፡
ጨዋታው ቀን 9 ሰዓት በአደማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር መረጃ ያመላክታል፡፡
የሸገር ደርቢ ባሳለፍነው ሕዳር 29 ቀን ሊደረግ የነበረ ቢሆንም…
ስፖርታዊ ጨዋነትን በመጣስ ሁከት የሚፈጥሩ ደጋፊዎችን ተጠያቂ ማድረግ እንደሚገባ ተገለጸ
አዲስ አበባ፣ ታኀሣስ 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ስፖርታዊ ጨዋነትን በመጣስ ያልተገባ ሁከት የሚፈጥሩ ደጋፊዎችን ተጠያቂ ማድረግ እንደሚገባ ተገለጸ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ከሊግ ካንፓኒ፣ ከከተማው የስፖርት ክለብ ደጋፊዎች፣ ከብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች እና ከመላው የስፖርት ቤተሰቦች ጋር በስፖርታዊ ጨዋነት ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል።
የአዲስ…
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል ከዌስትሃም እንዲሁም ቶተንሃም ከብራይተን የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ በበዓል ሰሞን መርሐ ግብር አርሰናል ከዌስትሃም እንዲሁም ቶተንሃም ከብራይተን ዛሬ ምሽት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
አርሰናል ከዌስትሃም ዩናይትድ የሚያደርጉት ጨዋታ ምሽት 5፡15 የሚደረግ ሲሆን በጨዋታው መድፈኞቹ የፕሪሚየርሊጉን መሪነት ከሊቨርፑል መልሰው ለመረከብ ወደ ሜዳ ይገባሉ፡፡
በጨዋታው…
ከ9ኛ እስከ 11ኛ ሳምንት የሚደረጉ የሊጉ መርሃ ግብሮች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን አይኖራቸውም ተባለ
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ9ኛ እስከ 11ኛ ሳምንት የሚደረጉ የሊጉ መርሃ ግብሮች የሱፐር ስፖርት የቀጥታ ስርጭት ሽፋን እንደማይኖራቸው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር አስታወቀ፡፡
ማህበሩ እንደገለፀው÷ የ9ኛ ሳምንት መርሃ ግብሮች ረቡዕ ታህሳስ 24 መካሄዳቸውን ሲቀጥሉ የቦታ ለውጥ አልተደረገባቸው፡፡
በመሆኑም ከ9ኛ እስከ 11ኛ…