ስፓርት
በፕሪሚየር ሊጉ ፋሲል ከነማ እና ሰበታ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል
አዲስ አበባ፣ግንቦት 10፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፐሪሚየርሊግ ፋሲል ከነማ መከላከያን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡
ሽመክት ጉግሳ እና ናትናኤል ገብረ ጊዮርጊስ የፋሲል ከነማን የድል ጎሎች ሲያስቆጥሩ አሚን ነስሩ ብቸኛዋን የመከላከያ ጎል አስቆጥሯል፡፡
ውጤቱን ተከትሎም ፋሲል ከነማ ደረጃውን ሲያስጠብቅ መከላከያ በነበረበት 8ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡
ረፋድ 4 ሰዓት በተከናወነ ጨዋታ ወራጅ ቀጠና የሚገኘው ሰበታ ከተማ ወልቂጤ ከተማን በተመሳሳይ 2 ለ 1 አሸንፏል።
Read More...
አዳማ ከተማ ከአሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ጋር በስምምነት ተለያየ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ያለፉትን አስር ጨዋታዎች በሊጉ ማሸነፍ ያልቻለው አዳማ ከተማ ከአሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ጋር በስምምነት ተለያየ፡፡
የዘንድሮ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከመጀመሩ በፊት አዳማ ከተማን ለማሰልጠን ፊርማውን ያኖረው አሠልጣኝ ፋሲል ተካልኝ÷ በዝውውር መስኮቱ ራሱን በማጠናከር ውድድር ቢጀምርም እስካሁን ከአራት…
በአማራ ሊግ እየተወዳደሩ ለሚገኙ ክለቦች የኳስ ድጋፍ ተደረገ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በአማራ እግር ኳስ ሊግ እየተወዳደሩ ለሚገኙ ክለቦች የኳስ ድጋፍ አደረገ፡፡
በአራት ምድብ ተከፍሎ እየተከናወነ የሚገኘው የአማራ ክልል ሊግ የምድብ አንድ ውድድር በኮምቦልቻ ከተማ እየተካሄደ ሲሆን÷ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንም ተሳታፊ ለሆኑ ክለቦች ኳስ ድጋፍ አድርጓል።…
በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በተደረገ ጨዋታ ባሕር ዳር ከተማ ድል ቀንቶታል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በተደረገ ጨዋታ ባሕር ዳር ከተማ አዳማ ከተማን 1 ለ 0 አሸነፈ፡፡
የጣናው ሞገድ ማሸነፉን ተከትሎ በ 29 ነጥብ ደረጃውን አሻስሎ 10ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ÷ ቡድኑ በተከታታይ ነጥብ መጣሉን ተከትሎ ትችት ውስጥ ለነበሩት አሰልጣኝ ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ የዛሬው ድል…
በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አዲስ አበባ ከተማና ድሬዳዋ ከተማ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) በ24ኛ ሳምነት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አዲስ አበባ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ አቻ ተለያይተዋል፡፡
ረፋድ 4 ሰዓት በተደረገው ጨዋታ ሪችሞንድ አዶንጎ ለአዲስ አበባ ከተማ ጎል ሲያስቆጥር ፥ ሄኖክ አየለ ለድሬዳዋ ከተማ ባለቀ ደቂቃ ማስቆጠር ችሏል፡፡
ቡድኖቹ ነጥብ መጋራታቸውን ተከትሎ አዲስ አበባ ከተማ ነጥቡን…
በፕሪሚየር ሊጉ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጅማ አባ ጅፋርን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሯል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ24ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከሰዓት በኋላ በተደረገ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጅማ አባ ጅፋርን አሸንፏል፡፡
ጨዋታውን ቅዱስ ጊዮርጊስ 1ለ 0 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ÷ብቸኛዋን የማሸነፊያ ግብ ጋቶች ፓኖም በቅጣት ምት በ57ኛ ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡
በፕሪሚየር ሊጉ ረፋድ ላይ በተደረገ ጨዋታ ሀድያ…
የኢትጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን በሴካፋ ዋንጫ ለሚሳተፉ 23 ተጨዋቾች ጥሪ አቀረበ
አዲስ አበባ፣ግንቦት 8፣2014 (ኤፍ ቢሲ) የኢትጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን በአሰልጣኝ ፍሬው ሀይለገብርኤል በኩል በዩጋንዳ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ለሚሳተፉ 23 ተጨዋቾች ጥሪ አቅርቧል፡፡
በዚህም መሰረት፡
ግብ ጠባቂ
ታሪኳ በርገና ፣ የምወድሽ ይርጋሽዋ እና ቤቴሌሄም ዮሀንስ
ተከላካይ
ቤቴሌሄም በቀለ፣ ብዙየሁ ታደሰ፣ አሳቤ ሞሶ፣ ቅድስት ዘለቀ፣…