ስፓርት
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፐሪሚየር ሊግ መሪው ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ ጣለ
አዲስ አበባ፣ግንቦት 4፣2014 (ኤፍ ቢሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በተካሄደ ጨዋታ መሪው ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ ጥሏል፡፡
ፈረሰኞቹ ረፋድ 4 ሰዓት በባህርዳር ስታዲየም ከወላይታ ዲቻ ጋር ባደረጉት ጨዋታ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡
ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ መጣሉን ተከትሎ የነጥብ ልዩነቱን ለማጥበብ እና ወደ ዋንጫ ፉክክር ለመመለስ የፋሲል ከነማ አሸናፊነት ተጠባቂ ነው፡፡
Read More...
አትሌት ለተሰንበት ግደይ በ2022 የቫሌንሺያ ማራቶን ላይ ትሳተፋለች
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 3 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ለተሰንበት ግደይ በ2022 የቫሌንሺያ ማራቶን ላይ ትሳተፋለች፡፡
በ5 ሺህ እና በ10 ሺህ ሜትሮች እንዲሁም በግማሽ ማራቶን የዓለም ክብረወሰንን የያዘችው አትሌት ለተሰንበት በ2022 የቫሌንሺያ ማራቶን ላይ እንደምትሳተፍ የዓለም አትሌቲክስ አስታውቋል።
አትሌቷ…
በፕሪሚየር ሊጉ ድሬዳዋ ከተማ ሀዲያ ሆሳዕናን በሰፊ የጎል ልዩነት አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ23ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ድሬዳዋ ከተማ ሀዲያ ሆሳዕናን በሰፊ የጎል ልዩነት አሸንፏል፡፡
ረፋድ 4 ሰዓት በተደረገው ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ ሀዲያ ሆሳዕናን 4 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት በማሸነፍ ወሳኝ 3 ነጥብ ከባህርዳር ስታዲየም ማግኘት ችሏል፡፡
ለድሬዳዋ ከተማ ሄኖክ…
ዋልያዎቹ የ2023 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታቸውን ግንቦት 25 ቀን ይጀምራሉ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ጨዋታ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ የሚያደርግባቸው ቀናት ይፋ ሆነዋል፡፡
የ2023 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ጨዋታዎች በዚህ ወር መካሄድ የሚጀምሩ ሲሆን÷ ኢትዮጵያ 2 ጨዋታዎችን የምታደርግበት ቀናት ታውቀዋል፡፡
በምድብ መ ከግብፅ፣ ጊኒ እና ማላዊ ጋር…
ካፍ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የሚያደርጋቸውን ጨዋታዎች ከሜዳው ውጭ እንዲያካሂድ ወሰነ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የአፍሪካ እግርኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በቀጣይ የሚያደርጋቸውን ጨዋታዎች ከሜዳው ውጭ እንዲያካሂድ ውሳኔ አሳልፏል፡፡
ከስድስት ወራት በፊት ‘‘ኢትዮጵያ በሜዳዋ ጨዋታዎችን ለማስተናገድ የሚያስችል እና የካፍን ደረጃ የሚያሟላ ስታዲየም የላትም’’ በሚል በሜዳዋ ማድረግ የሚገባትን ጨዋታዎች በገለልተኛ ሜዳ…
አትሌት ፀሐይ ገመቹ በሊዝበን ግማሽ ማራቶን ድል ተቀዳጀች
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) አትሌት ፀሐይ ገመቹ በፖርቹጋል ዋና ከተማ ሊዝበን በተካሄደው የግመሽ ማራቶን ውድድር ለሁለተኛ ጊዜ አሸነፈች፡፡
አትሌቷ የሊዝበንን ግማሽ ማራቶን ርቀት 1 ሰዓት ከ06 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቃለች፡፡
ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ጎይተይቶም ገብረ ስላሴ 1 ሰዓት ከ06 ደቂቃ 45…
ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ጠረጴዛ ቴኒስ ሻምፒዮና ሰባት ሜዳሊያዎችን አገኘች
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ሲካሄድ በቆየው የምሥራቅ አፍሪካ የጠረጴዛ ቴኒስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ሰባት ሜዳሊያዎችን በማግኘት አጠናቀቀች።
ከሚያዚያ 27 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ዘጠኝ አገራት የተሳተፉበት ውድድር ለአራት ተከታታይ ቀናት በአዲስ አበባ ከተማ የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ተካሂዷል።
በዚህ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ጠረጴዛ ቴኒስ…