ስፓርት
ፌዴሬሽኑ ለአፍሪካ ዋንጫ ላለፉት ዋልያዎቹ 6 ሚሊየን ብር ሽልማት ለማበርከት ወሰነ
አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 19 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ከ8 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ለለተመለሰው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ( ዋልያዎቹ) አባላት የ6 ሚሊየን ብር ሽልማት እንዲሰጣቸው ውሳኔ አሳለፈ።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የተለያዩ ውሳኔዎች ማስተላለፉን ከፌዴሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በዚህም ለዋልያዎቹ የተበረከተው ሽልማት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማጠቃለያዉን በሚያደርግበት ሐዋሳ ከተማ እንዲሆን ወስኗል።
በተመሳሳይ ለክልል እግር ኳስ…
Read More...
በፕሪሚየር ሊጉ ሃዲያ ሆሳዕና ከድሬዳዋ አቻ ተለያይተዋል
አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 18 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በ21ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ምሽት አንድ ሰአት ላይ ሃዲያ ሆሳዕና ከድሬዳዋ ከተማ ተጫውተዋል፡፡
ጨዋታው ያለምንም ጎል በአቻ ውጤት ተጠናቋል፡፡
10 ሰአት ላይ በተደረገ ጨዋታ ሰበታ ከተማ ባህር ዳር ከተማን ማሸነፉ ይታወሳል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦…
በፕሪሚየር ሊጉ ሰበታ ከተማ ባህር ዳር ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 18 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በ21ኛው ሳምንት የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሰበታ ከተማ ባህር ዳር ከተማን 2 ለ 1 አሸነፈ፡፡
ጨዋታውን ባህር ዳር ከተማ የሰበታው ሃይለሚካኤል ራሱ ላይ ባስቆጠራት ጎል 1 ለ 0 መምራት ቢችልም ሰበታ ከተማ ከመመራት ተነስቶ ባስቆጠራቸው ጎሎች አሸንፎ ወጥቷል፡፡
ፍጹም ገብረማርያም እና ዱሬሳ ሹቢሳ ለሰበታ…
ኢትዮጵያ ቡና የስነ ምግባር ጥሰት በፈፀሙ አራት ተጫዋቾች ላይ ቅጣት አስተላለፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤት ኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ስኬታማ የውድድር ዘመን እያሳለፈ የሚገኘው ኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ የስነ ምግባር ጥሰት በፈፀሙ አራት ተጫዋቾች ላይ ቅጣት አስተላለፈ።
ታፈሰ ሠለሞን ፣ሚኪያስ መኮንን ፣ አዲስ ፍስሃ እና ሀይሌ ገ/ተንሳይ ድሬዳዋ የክለቡ ተጨዋቾች ከሚያድሩበት ሆቴል በመውጣት ባልተገባ…
አርባምንጭ ከተማ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ መመለሱን አረጋገጠ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አርባምንጭ ከተማ ወደ ፕሪምየር ሊግ ማደጉን በዛሬው ዕለት አረጋግጧል።
በከፍተኛ ሊጉ ምድብ ሐ ተወዳዳሪ የሆነው አርባምንጭ ከተማ የ21ኛ ሳምንት ጨዋታውን ነገ የሚያደርግ ቢሆንም ተከታዩ ኮልፌ በቡታጅራ መሸነፉን ተከትሎ ወደ 2014 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን ማረጋገጡን ሶከር ኢትዮጵያ ዘግቧል።
በ2004…
የኢትዮጵያ ውሃ ስፖርቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንቱን አሰናበተ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)የኢትዮጵያ ውሃ ስፖርቶች ፌዴሬሽን ትናንት ባካሄደው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት የነበሩትን አቶ ተሾመ ሶርሳን አሰናብቷል ።
በቅርቡ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ያካሄደውን የስራ አስፈፃሚ ምርጫ ላይ ምርጫው ህገወጥ በመሆኑ የአትዮጵያ ውሃ ስፖርት ፌዴሬሽንን በመወከል በምርጫው የሚሳተፍ ስራ…
አዳማ ከተማ በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ ባስቆጠራት ግብ ከወልቂጤ ጋር ነጥብ ተጋርቷል
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 15፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በቤት ኪንግ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ወልቂጤ ከተማ ከአዳማ ከተማ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።
1 ለ 0 ሲመሩ የነበሩት ወልቂጤ ከተማዎች በ90ኛው ደቂቃ ላይ በተቆጠረባቸው ግብ ከአዳማ ከተማ ጋር ነጥብ ተጋርተዋል።
ወልቂጤ ከተማዎች በረመዳን የሱፍ ግብ እረፍት ከመውጣታቸው በፊት 45ኛው ደቂቃ ላይ…