Fana: At a Speed of Life!

አቶ ሽመልስ አብዲሳ በኒንዢያ ግዛት የቻይና ኮሙኒስት ፓርቲ ፀሐፊ ጋር መከሩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል ርዕሠ-መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በኒንዢያ ግዛት የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ፀሐፊ ሊያንግ ያንሹን ጋር ተወያዩ።

በኦሮሚያ ፕሬዚዳንት ፅኅፈት ቤት በተካሄደው ውይይት በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዥዩዋንን ጨምሮ የተለያዩ አካላት ተገኝተዋል፡፡

ሁለቱ ወገኖች በባሕል፣ በቋንቋና በምጣኔ ሐብት ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ከኦሮሚያ ርዕሰ መስተዳድር ጽኅፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

አቶ ሽመልስ ፥ ኢትዮጵያ የምታካሂደውን የልማት ሥራ ለማፋጠን እና ምጣኔ ሐብቷን ለማሳደግ “የቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ” ሚና ከፍተኛ እንደሆነ አንስተውላቸዋል፡፡

ኢትዮጵያ ኢኒሼቲቩን ዕውን በማድረግ ረገድ የቻይናን ጠንካራ ድጋፍ ትፈልጋለችም ነው ያሉት፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.