Fana: At a Speed of Life!

በተለያዩ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የ8ኛ ክፍል ፈተና እየተሰጠ ነው

 

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በተለያዩ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የ8ኛ ክፍል ፈተና ዛሬ መሰጠት ተጀምሯል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ 75 ሺህ 100 የ8ኛ ክፍል ተፈታኞች÷ በ182 የመፈተኛ ጣቢያ እየተፈተኑ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ቅኝት ባደረገበት በልደታ ክፍለከተማ በሚገኘው የተስፋ ኮከብ ትምህርት ቤት ፈተናው በሰላማዊ መንገድ እየተሰጠ መሆኑን አረጋግጧል።

በተመሳሳይ በአማራ፣ ደቡብ፣ ጋምቤላ፣ ቤኒሻንጉል-ጉሙዝ እና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሎች የ8ተኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና መሰጠት መጀመሩን የክልሎቹ ትምህርት ቢሮዎች አስታውቀዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.