በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 10 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው፡፡
ሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክን ጨምሮ በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ከ3 ነጥብ 1 ሚሊየን በላይ ችግኞች ይተከላሉ ተብሏል፡፡
ከዚህ ውስጥ 138 ሺህ በላይ የሚሆኑት የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሆኑ የዞኑ ግብርና መምሪያ ምክትል ሃላፊ አቶ ዮሃንስ ይግዛው ተናግረዋል፡፡
በኤልያስ አንሙት