Fana: At a Speed of Life!

በዓዲ-ዳዕሮ ከተማ 18 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ለአገልግሎት በቃ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 1፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በትግራይ ክልል የዓዲ-ዳዕሮ ከተማ 18 ሺህ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት መስጠት መጀመሩን በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የውሃና ኢነርጂ ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ተወካይ ኃላፊ ኢንጂነር ዮሃንስ መለሰ በዚህ ወቅት÷ የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክት ግንባታው ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው ዋን ዋሽ ኢንተርናሽናል ከተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት በተገኘ 57 ሚሊየን ብር ወጪ ነው።

ፕሮጀክቱ ከ6 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር በላይ የቁፋሮ እና የውኃ ቱቦ መስመር ዝርጋታ ሥራዎችን በማከናወን ለአገልግሎት እንዲበቃ መደረጉ ተገልጿል፡፡

የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ 18ሺህ 500 የሚሆኑ የዓዲ ዳዕሮ ከተማና አካባቢዋ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ መገለጹን ኢዜአ ዘግቧል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.