የዘላቂ ልማት ግቦች የስትሪንግ ኮሚቴ ስብሰባ ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ የዘላቂ ልማት ግቦች የስትሪንግ ኮሚቴ ስብሰባ መካሄዱን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አስታውቋል።
ስብሰባውን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) እና በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ድጋፍ አስተባባሪ ራሚዝ አላክባሮቭ እንደመሩት ተገልጿል።
በስብሰባው ላይ ሚኒስትሮችና የልማት አጋሮች ኃላፊዎች የተሳተፉ ሲሆን፥ የኢትዮጵያን የዘላቂ ልማት ግቦች ትግበራ ለማፋጠን ወሳኝ መሆኑን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል።