Fana: At a Speed of Life!

አርሰናል በበርንማውዝ ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በሜዳው ኤሚሬትስ ስታዲየም በርንማውዝን ያስተናገደው አርሰናል 2 ለ 1 ተሸንፏል፡፡

የበርንማውዝን የማሸነፊያ ግቦች ዲያን ሁጅሰንና ኢቫኒልሰን ሲያስቆጥሩ አርሰናልን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ደግሞ ዲክላን ራይስ ከመረብ አሳርፏል፡፡

ቀደም ብለው በተደረጉ ጨዋታዎች አስቶንቪላ ፉልሃምን 1 ለ 0 እንዲሁም ሌስተር ሲቲ ሳውዝሃምፕተንን 2 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡

በሌላ በኩል ኤቨርተን እና ኢፕስዊች ታውን ያረጉት ጨዋታ 2 ለ 2 በሆ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.